እንዳሁኑ ሳይሆን ፤
በፍቅርሽ ሰምጬ አንድላይ እንዳለን ፤
ለብቻ መሆኔ ሳይከሰት በፊት ፤
ፍቅርን እያመለክሁ በመዉደድሽ ግፊት ፤
እኔ ባይገባኝም፤
በዉሸት ገፅታሽ በክህደት አባዜ ፤
ባንች ለመጠለል እንዳራቅሁ ከወንዜ ፤
ያኔ በፍቅራችን አንች ብልህ ነበርሽ እኔ ደግሞ ሞኙ፤
አንች ሽርሙጥና እኔ ግን ለመኖር በፍቅር ካታኙ።
ዛሬ ግን፤
አይንሽ እንዲጠፋ እግርሽ እንዲቆረጥ ለአምላኬ ባልከስም፤
ወጦልኝ ነቅቼ መከተል አቆምሁኝ አንችን አልመኝም።
እሱባለው ቸኮል